ህትመቶች

ደንብ ቁጥር 206/2018 የመንግሥት ሠራተኞች የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ተቋም ሥልጣንና ተግባር፣አደረጃጀት

image description

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግሥት መሥሪያ  ቤቶች ውስጥ ብቃትን መሠረት ያደረገ የሰው ሀብት ሥራ  አመራር እና ልማት የአሰራር ሥርዓት መዘርጋትና  ተግባር ላይ ማዋል በማስፈለጉ፤   የከተማ አስተዳደሩ የመንግሥት ሠራተኞች በዕውቀት፣  በክህሎት እና መልካም ባህሪያት እንዲታነጹ  እና  ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል የብቃት ምዘና እና  ማረጋገጫ የአሰራር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ  በመሆኑ፤  የመንግሥት ሠራተኛ የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ሥራዎችን በግልጽነት፣ በቅንጅት፣ ወጥ በሆነ መንገድ በመተግበር እና ተጠያቂነትን በማረጋገጥ እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ቅልጥፍናን በማሻሻል የዜጎችን እርካታ እና በተቋማት ላይ ያላቸውን አመኔታ ለማሳደግ ሲባል የብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ተቋም ሥልጣንና ተግባር፣ አደረጃጀት እና አሰራሩን በሕግ መወሰን አስፈላጊነቱ በመታመኑ፤ የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ በከተማው አስተዳደር የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር ፹፯/፪ሺ፲፯ አንቀጽ ፲፯ ንዑስ አንቀጽ (፪) በተደነገገው መሰረት ይህን ደንብ አውጥቷል፡፡